Telegram Group & Telegram Channel
.................አድዋ..............

✍🏽.አጤ ዮሐንስ ካረፋ በኋላ ግዛታቸውን እያስፋፉ ውጫሌው በተባለው ስፍራ ላይ ሰፍረው ሳለ ሚያዚያ 25 ቀን 1881 ከኢጣሊያ መንግስት ጋር 20 አንቀፆችን ተዋዋሉ ውሉም "የውጫሌው ውል" ተባለ።ይሄንንም ሲፈርሙ ገና አልነገሱም ነበር።ከእነዚህም 20 አንቀፆች ውስጥ በአንቀፅ 17 አለመስማማት ተፈጠረ።ይህም አንቀፅ በሁለት ግልባጭ የተፃፈ ነበር በአማርኛ እና በጣሊያነኛ።
1.በአማርኛ የተፃፈው "የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ከውጭ ሀገር መንግስታት ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት 'ፈቃዱ ከሆነ' በኢጣሊያ መንግስት በኩል ሊያደርግ ይቻለዋል"
2.ነገር ግን በኢጣሊ "የኢትዮጵያ መንግስት ከውጭ ሀገር መንግስታት ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት በኢጣሊያ መንግስት አማካኝነት ማድረግ ይገባዋል"የሚል ነበር።
✍🏽.አጤ ምኒሊክ እንደዚህ ተብሎ መተርጎሙን ያወቁት ንጉሠ ነገሥት ከሆኑ በኋላ የደስታ መልዕክታቸውን ለአውሮፓ መንግስት ሊልኩ ሲል አይ ደብዳቤ ቢሆንም በእኛ በኩል ነው ማለፍ ያለበት ባሉ ጊዜ ነው።
✍🏽.ጣልያኖችም በዮሐንስ ጊዜ ሲያደርጉት እንደነበረው አሁንም የተለያዩ መኳንቶች ከእነ ራስ አሉላ ጋር ተጣልተው ወደ እነሱ እንዲመጡ አደረጉ የጣሊያን ጦር በእነዚህ መኳንት እየተመራ ብዙ ቦታዎችን ተቆጣጠረ
✍🏽.አጤ ምኒሊክም ለቀው እንዲወጡ ቢያስጠነቅቁም አሻፈረኝ አሉ።አጤ ምኒሊክም አዋጅ አሰነገሩ አዋጁም"የሐገሬ ሰው ከአሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም።አንተም እስከ አሁን አላስቀየምከኝም።አሁንም ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ጉልበትየሌለህ ለልጅህ:ለሚስትህ:ለሀይማኖትህ እና ለሐገርህ ስትል በሐዘንህ እርዳኝ ።የወሰለትክ እንደሆነ ግን ትጣላኛለህ አልተውህም ።እግዝዕትነ ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም ዘመቻዬም በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ"ብለው የክተት አዋጅ መስከረም 7 ቀን 1988 ዓ.ም አወጁ።
✍🏽."እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም ግን እንዲህ መሳዩን ውል አልቀበልም እኛ የናንተን የበላይነት አንፈልግም አንፈራችሁም።"እቴጌ ጣይቱ ብርሐን ዘኢትዮጵያ የውጫሌውን ውል በተመለከተ የተናገሩት።
-ጥቅምት 2 ቀን 1888 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ሲነሱ እቴጌ ጣይቱ አብረው ተነሱ ።ራስ መኮንን የጦር አበጋዝ ሆነው ራስ ወሌን :ራስ ሚካኤልን:ራስ መንገሻን ወ.ዘ.ተ ይዘው ጣሊያኖች በመሸጉት አምባላጌ ተራራ ላይ ሠፈሩ።
-ህዳር 28 አምባላጌ ላይ የተደረገው ጦርነት 2 ሰዓት ፈጅቶ ራስ መኮንን በመሩት ጦር የኢጣሊያ ጦር ወደ መቀሌ ሸሸ።ራስ መኮንን እየገሰገሱ ወደ መቀሌ ከተጓዙ በኋላ መቀሌ ላይ የተካሄደው ጦርነት ብዙ ሰዓት ከፈጀ በኋላ የውሃ ጥም ተጨምሮባቸው ብዙ መሳሪያዎችን አስረክበው ሸሹ።
-ከእነዚህ ጦርነቶች በኋላ ዋና የጦር አዝማቹ ባራቴሪ የቀረውን ጦር በ4 አቅጣጫ ከፍሎ አሰለፉ።
1.ጄ/ል አርሞንዲ
2.ጄ/ል ዳቦርሚዳን
3.ጄ:ል አልበርቶኒ
4.ጄ/ል ኤሌና የጦር ካርታ አዘጋጅቶ አሰለፋቸው።አጠቃላይ የኢጣሊ ጦር ከ20 ሺህ የበለጠ እና በዘመናዊ የጦር መሳሪያ የተሞላ እና 60 መድፎችን ታጥቀው ቀረቡ።
-የኢትዮጵያ ሰራዊት ደግሞ በ10 ጀነራሎች የተዋቀረ ነበር።
1.ምኒሊክ ከአድዋ አጠገብ ከ30,000 ሰራዊት ጋር
2.ጣይቱ በዚሁ ስፍራ ከ3000 ወታደር ጋር
3.ተክለ ሐይማኖት በዚሁ ስፍራ ከ3000 ወታደር ጋር
4.ፊት አውራሪ ገበየው ገቦ ከአሰም ወንዝ ተሻግሮ ከ6000 ወታደር ጋር
5.ንጉስ ሚካኤል ከ8000 ወታደር ጋር
6.ራስ መኮንን ከ8000 ወታደር ጋር
7.ራስ መንገሻ ዮሐንስ ከራስ አሉላ እና ከራስ ሐጎስ ጋር ከ3000 ወታደር
8.ዋግስዩም ከ6000 ወታደር ጋር
9.ራስ ወሌ ከ3000 ወታደር ጋር
10.ራስ መንገሻ አቲከም ከ3000 ወታደር ጋር በድምሩ 73,000 የኢትዮጵያ ሰራዊት ለውጊያ ተሰልፎ ነበር በዚህ ሰዓት የጊወርጊስ ዕለት ስለነበር ታቦቱን ይዘው እንደ ተሰለፉ ይተረካል።በጦርነቱ ጊዜም ቅዱስ ጊዎርጊስም ወርዶ ተዋግቷል ይባላል።ጦርነቱም ከተጀመረ በኋላ በሁለቱም ወገን ብዙ እልቂት ደረሰ።ጦርነቱም አንድ ሙሉ ቀን ወሰደ።
-ከኢጣሊ ወገን 5000 ነጭ:2000 ከኤርትራ የተመለመሉ ወታደሮች ሲሞቱ:2400 የሚሆኑት ከ60 መድፍ እና ከብዙ መሳሪያዎች ጋር ተማርከዋል።
-በኢትዮጵያ በኩል ህዝቡ ተኝቶ መታኮስ የፈሪ ነው እያለ ቆሞ በጀግንነት ሲዋጋ ስለነበር ለጥይት የተጋለጠ ስለነበር ብዙ ሰው አልቋል።በአጠቃላይ 10,000 እንደነበር ብዙዎች ይስማማሉ።
-ከ4ቱ መሪዎች 2ቱ ጄ/ል ዳቦር እና አርሞንዲን ተገደሉ።ጄ/ል አሌና ቆሰለ :አልበርቶኒ ተማረከ።በዚህም ጦርነት ትልቁን ድርሻ ባሻይ አውኣሎም በስለላ ተወጧል።
✍🏽.ጦርነቱም በባሻይ አውኣሎም ብልሀትነት:በምኒሊክ የጦር አደረጃጀት:በጣይቱ የተለየ ዘዴ እና በእነ ራስ መኮንን የጦር መሪነት እንዲሁም በኢትዮጵያ ህዝብ ወኔ እና ጀግንነት ጦርነቱን በድል አጠናቀቀች።
✍🏽.የዓለም ህዝብም ጉድ አለ።ኢጣሊ አንገተቷን ደፋች መላው የአፍሪካ ህዝብ አንገት ደግሞ ቀና አለ በዚሁም በወቅቱ የነበረው የኢጣሊ ጠ/ሚ ፍራንቺስኮ ክርስፒ ከስልጣናቸው ወረዱ።ለመላው አፍሪካዊያን ደግሞ የብርሃን ጮራ ብቅ አለች።ከድሉም በኋላ
"ምኒሊክ ተወልዶ በያነሳ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ ሐበሻ" እየተባለ ተዘመረለት።



🙏🏾.ክብር አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍሰው ይቺን ሀገር ላቆሙ የኢትዮጵያ ነገስታት እና ህዝቦች

.ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

@yekidst_hager777
@yekidst_hager777
@yekidst_hager777



tg-me.com/yekidst_hager777/2484
Create:
Last Update:

.................አድዋ..............

✍🏽.አጤ ዮሐንስ ካረፋ በኋላ ግዛታቸውን እያስፋፉ ውጫሌው በተባለው ስፍራ ላይ ሰፍረው ሳለ ሚያዚያ 25 ቀን 1881 ከኢጣሊያ መንግስት ጋር 20 አንቀፆችን ተዋዋሉ ውሉም "የውጫሌው ውል" ተባለ።ይሄንንም ሲፈርሙ ገና አልነገሱም ነበር።ከእነዚህም 20 አንቀፆች ውስጥ በአንቀፅ 17 አለመስማማት ተፈጠረ።ይህም አንቀፅ በሁለት ግልባጭ የተፃፈ ነበር በአማርኛ እና በጣሊያነኛ።
1.በአማርኛ የተፃፈው "የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ከውጭ ሀገር መንግስታት ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት 'ፈቃዱ ከሆነ' በኢጣሊያ መንግስት በኩል ሊያደርግ ይቻለዋል"
2.ነገር ግን በኢጣሊ "የኢትዮጵያ መንግስት ከውጭ ሀገር መንግስታት ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት በኢጣሊያ መንግስት አማካኝነት ማድረግ ይገባዋል"የሚል ነበር።
✍🏽.አጤ ምኒሊክ እንደዚህ ተብሎ መተርጎሙን ያወቁት ንጉሠ ነገሥት ከሆኑ በኋላ የደስታ መልዕክታቸውን ለአውሮፓ መንግስት ሊልኩ ሲል አይ ደብዳቤ ቢሆንም በእኛ በኩል ነው ማለፍ ያለበት ባሉ ጊዜ ነው።
✍🏽.ጣልያኖችም በዮሐንስ ጊዜ ሲያደርጉት እንደነበረው አሁንም የተለያዩ መኳንቶች ከእነ ራስ አሉላ ጋር ተጣልተው ወደ እነሱ እንዲመጡ አደረጉ የጣሊያን ጦር በእነዚህ መኳንት እየተመራ ብዙ ቦታዎችን ተቆጣጠረ
✍🏽.አጤ ምኒሊክም ለቀው እንዲወጡ ቢያስጠነቅቁም አሻፈረኝ አሉ።አጤ ምኒሊክም አዋጅ አሰነገሩ አዋጁም"የሐገሬ ሰው ከአሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም።አንተም እስከ አሁን አላስቀየምከኝም።አሁንም ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ጉልበትየሌለህ ለልጅህ:ለሚስትህ:ለሀይማኖትህ እና ለሐገርህ ስትል በሐዘንህ እርዳኝ ።የወሰለትክ እንደሆነ ግን ትጣላኛለህ አልተውህም ።እግዝዕትነ ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም ዘመቻዬም በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ"ብለው የክተት አዋጅ መስከረም 7 ቀን 1988 ዓ.ም አወጁ።
✍🏽."እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም ግን እንዲህ መሳዩን ውል አልቀበልም እኛ የናንተን የበላይነት አንፈልግም አንፈራችሁም።"እቴጌ ጣይቱ ብርሐን ዘኢትዮጵያ የውጫሌውን ውል በተመለከተ የተናገሩት።
-ጥቅምት 2 ቀን 1888 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ሲነሱ እቴጌ ጣይቱ አብረው ተነሱ ።ራስ መኮንን የጦር አበጋዝ ሆነው ራስ ወሌን :ራስ ሚካኤልን:ራስ መንገሻን ወ.ዘ.ተ ይዘው ጣሊያኖች በመሸጉት አምባላጌ ተራራ ላይ ሠፈሩ።
-ህዳር 28 አምባላጌ ላይ የተደረገው ጦርነት 2 ሰዓት ፈጅቶ ራስ መኮንን በመሩት ጦር የኢጣሊያ ጦር ወደ መቀሌ ሸሸ።ራስ መኮንን እየገሰገሱ ወደ መቀሌ ከተጓዙ በኋላ መቀሌ ላይ የተካሄደው ጦርነት ብዙ ሰዓት ከፈጀ በኋላ የውሃ ጥም ተጨምሮባቸው ብዙ መሳሪያዎችን አስረክበው ሸሹ።
-ከእነዚህ ጦርነቶች በኋላ ዋና የጦር አዝማቹ ባራቴሪ የቀረውን ጦር በ4 አቅጣጫ ከፍሎ አሰለፉ።
1.ጄ/ል አርሞንዲ
2.ጄ/ል ዳቦርሚዳን
3.ጄ:ል አልበርቶኒ
4.ጄ/ል ኤሌና የጦር ካርታ አዘጋጅቶ አሰለፋቸው።አጠቃላይ የኢጣሊ ጦር ከ20 ሺህ የበለጠ እና በዘመናዊ የጦር መሳሪያ የተሞላ እና 60 መድፎችን ታጥቀው ቀረቡ።
-የኢትዮጵያ ሰራዊት ደግሞ በ10 ጀነራሎች የተዋቀረ ነበር።
1.ምኒሊክ ከአድዋ አጠገብ ከ30,000 ሰራዊት ጋር
2.ጣይቱ በዚሁ ስፍራ ከ3000 ወታደር ጋር
3.ተክለ ሐይማኖት በዚሁ ስፍራ ከ3000 ወታደር ጋር
4.ፊት አውራሪ ገበየው ገቦ ከአሰም ወንዝ ተሻግሮ ከ6000 ወታደር ጋር
5.ንጉስ ሚካኤል ከ8000 ወታደር ጋር
6.ራስ መኮንን ከ8000 ወታደር ጋር
7.ራስ መንገሻ ዮሐንስ ከራስ አሉላ እና ከራስ ሐጎስ ጋር ከ3000 ወታደር
8.ዋግስዩም ከ6000 ወታደር ጋር
9.ራስ ወሌ ከ3000 ወታደር ጋር
10.ራስ መንገሻ አቲከም ከ3000 ወታደር ጋር በድምሩ 73,000 የኢትዮጵያ ሰራዊት ለውጊያ ተሰልፎ ነበር በዚህ ሰዓት የጊወርጊስ ዕለት ስለነበር ታቦቱን ይዘው እንደ ተሰለፉ ይተረካል።በጦርነቱ ጊዜም ቅዱስ ጊዎርጊስም ወርዶ ተዋግቷል ይባላል።ጦርነቱም ከተጀመረ በኋላ በሁለቱም ወገን ብዙ እልቂት ደረሰ።ጦርነቱም አንድ ሙሉ ቀን ወሰደ።
-ከኢጣሊ ወገን 5000 ነጭ:2000 ከኤርትራ የተመለመሉ ወታደሮች ሲሞቱ:2400 የሚሆኑት ከ60 መድፍ እና ከብዙ መሳሪያዎች ጋር ተማርከዋል።
-በኢትዮጵያ በኩል ህዝቡ ተኝቶ መታኮስ የፈሪ ነው እያለ ቆሞ በጀግንነት ሲዋጋ ስለነበር ለጥይት የተጋለጠ ስለነበር ብዙ ሰው አልቋል።በአጠቃላይ 10,000 እንደነበር ብዙዎች ይስማማሉ።
-ከ4ቱ መሪዎች 2ቱ ጄ/ል ዳቦር እና አርሞንዲን ተገደሉ።ጄ/ል አሌና ቆሰለ :አልበርቶኒ ተማረከ።በዚህም ጦርነት ትልቁን ድርሻ ባሻይ አውኣሎም በስለላ ተወጧል።
✍🏽.ጦርነቱም በባሻይ አውኣሎም ብልሀትነት:በምኒሊክ የጦር አደረጃጀት:በጣይቱ የተለየ ዘዴ እና በእነ ራስ መኮንን የጦር መሪነት እንዲሁም በኢትዮጵያ ህዝብ ወኔ እና ጀግንነት ጦርነቱን በድል አጠናቀቀች።
✍🏽.የዓለም ህዝብም ጉድ አለ።ኢጣሊ አንገተቷን ደፋች መላው የአፍሪካ ህዝብ አንገት ደግሞ ቀና አለ በዚሁም በወቅቱ የነበረው የኢጣሊ ጠ/ሚ ፍራንቺስኮ ክርስፒ ከስልጣናቸው ወረዱ።ለመላው አፍሪካዊያን ደግሞ የብርሃን ጮራ ብቅ አለች።ከድሉም በኋላ
"ምኒሊክ ተወልዶ በያነሳ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ ሐበሻ" እየተባለ ተዘመረለት።



🙏🏾.ክብር አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍሰው ይቺን ሀገር ላቆሙ የኢትዮጵያ ነገስታት እና ህዝቦች

.ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

@yekidst_hager777
@yekidst_hager777
@yekidst_hager777

BY ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/yekidst_hager777/2484

View MORE
Open in Telegram


ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Importantly, that investor viewpoint is not new. It cycles in when conditions are right (and vice versa). It also brings the ineffective warnings of an overpriced market with it.Looking toward a good 2022 stock market, there is no apparent reason to expect these issues to change.

Spiking bond yields driving sharp losses in tech stocks

A spike in interest rates since the start of the year has accelerated a rotation out of high-growth technology stocks and into value stocks poised to benefit from a reopening of the economy. The Nasdaq has fallen more than 10% over the past month as the Dow has soared to record highs, with a spike in the 10-year US Treasury yield acting as the main catalyst. It recently surged to a cycle high of more than 1.60% after starting the year below 1%. But according to Jim Paulsen, the Leuthold Group's chief investment strategist, rising interest rates do not represent a long-term threat to the stock market. Paulsen expects the 10-year yield to cross 2% by the end of the year. A spike in interest rates and its impact on the stock market depends on the economic backdrop, according to Paulsen. Rising interest rates amid a strengthening economy "may prove no challenge at all for stocks," Paulsen said.

ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ from us


Telegram ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ
FROM USA